ኢኮኖሚ


ኢትዮጵያ ቡና (የቡና ፍሬ) ፣ የዘይት ዘሮች እና ቅመማ ቅመሞች የሚሰበሰብበት ለም መሬት አላት። ቡና ከወጪ ንግድ 60 በመቶውን የያዘ እንደ መጀመሪያው የተፈጥሮ ሀብት ይቆጠራል፣ እንዲሁም 85% የሚሆነው ህዝብ በግብርና ውስጥ ይሠራል። ኢትዮጵያ ነዳጅ እና ነባር ምርቶችን፣ የምግብ ምርቶችን፣ የህክምና፣ የኤሌክትሪክ እና የፕላስቲክ መሳርያዎችን፣ ከባድ መሳሪያዎችን፣ የእርሻ መሳሪያዎችን፣ የምግብ ዘይት፣ ስኳር፣ ስንዴን እና የግንባታ ቁሳቁሶችን ከውጭ ታስገባለች። በማዕድን ዘርፍም እንደ ወርቅ ያሉት ላይ ሰፊ ክምችት አላት።

ኢትዮጵያ በሁሉም ኢኮኖሚያዊ መስኮች ትኩረት በማድረግ፤ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች በሀግሪቱ ላይ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያሳድጉ ለማሳመን ሰፊ የልማት ማሻሻያ አካሂዳለች። የውጭ ባለሐብቶች በተፈቀደላቸው ዘርፎች (አገልግሎቶችን ከማማከር እና ከወረቀት ህትመት መስኮች በስተቀር) የንግድ ሥራ ፕሮጀክት ማቋቋም ከፈለገ ፕሮጄክቶችን ለማስጀመር በአስተናጋጁ ሀገር (ኢትዮጵያ) ከ 100 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በታች የማይሆን የገንዘብ መጠን ማቅረብ ይጠበቅበታል። እንደ ችርችሮ እና ጅምላ ንግድ ፣ አስመቺና ላኪ ንግድ፣ የመጓጓዣ አገልግሎቶች፣ የቱሪዝም ኤጄንሲዎች እና አንዳንድ ሌሎች አገልግሎቶችን የመሰሉ ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች የተገደቡ ናቸው። መንግስት ለውጭ ባለሀብቶች ካቀረባቸው ዋና ዋና ዋስትናዎች መካከል ከተለያዩ በጣምራ ከተሰሩ የንግድ ፕሮጄክቶች የሚገኝ ካፒታልናን ትርፍን መመልስ፣ ከኢንቨስትመንትና ንግድ የሚያገኛቸው ትርፎችና ጥቅማጥቅሞች እና ሌሎች የካሳ ክፍያ ይገኙበታል።


በኢትዮጵያ ስለኢንቨስትመንት የበለጠ መረጃ ለማግኘት እባክዎን የኢንቨስትመንት ባለስልጣን ድረ-ገጽን ይጎብኙ፡

http://www.investethiopia.gov.et/