የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን


የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን እ.ኤ.አ. በ 1958 በአፍሪካ ሀገራት አባላት መካከል ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት የተቋቋመ ሲሆን ከአምስት የ ECOSOC ቀጠናዊ ኮሚሽኖች ውስጥ አንዱ ነው። ኮሚሽኑ በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነው፦

  • ማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲና አስተዳደር
  • ክልላዊ ውህደት እና ንግድ
  • የግሉ ሴክተር ልማት እና ፋይናንስ
  • መረጃ እና ስታቲስቲክስ
  • ቴክኖሎጂ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የተፈጥሮ ሀብት አያያዝ
  • ·• ሥርዓተ-ጾታ፣ ድህነት እና ማህበራዊ ፖሊሲ
  • ·• የኢኮኖሚ ልማት እና ዕቅድ

እንዲሁም ሌሎች አምስት የክልል ጽ/ቤቶች አሉ (SROs):

  • ሰሜን አፍሪካ (ሞሮኮ)
  • ምዕራብ አፍሪካ (ኒጀር)
  • መካከለኛው አፍሪካ (ካሜሩን)
  • ምስራቅ አፍሪካ (ሩዋንዳ)
ደቡብ አፍሪካ (ዛምቢያ)