ባህልና ልማድ


የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር ወደ 114 ሚሊዮን (2020 እስታትስቲክስ) የሚገመት ሲሆን ከናይጄሪያ ቀጥሎ በአፍሪካ ሁለተኛው ይደርገዋል። አዲስ አበባን “የአፍሪካ ፖለቲካዊ ዋና ከተማ” በመባል ትታወቃለች። ኢትዮጵያ እያንዳንዳቸው የራሳቸው ባህል፣ ልማድ እና 80 የሚያህሉ ቋንቋ ወይም አንዳቸውን ከሌላው የሚለይ ዘዬ ያሏቸው ብሄረሰቦችን ይዛለጭ

የኢትዮጵያ ባህል ከአፍሪካ ለየት ያለ ነው። የአይሁድ እምነት፣ ክርስትና እና እስልምና ተጽዕኖ ያረፈበት፤ እንዲሁም በአቢሲኒያ መንግሥት እና በጥንቷ የመን እና በጥቢቡ ሰለሞን መንግሥት መካከል ቁርኝት የፈጠረ ወግ ያዘለ ነው።

በኢትዮጵያ ባህላዊ እና ልማዳዊ ዳንስ ለየት ያለ ሲሆን፤ ልዩ ባህላዊ አልባሳት የሚለብሱበት እንደ ሰርግ ባሉ ማህበራዊ ዝግጅቶች ውስጥ ይገለጻል ፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ ብሔረሰቦች በራሳቸው ባህል እና ወግ ይወከላሉ።

የንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ወደ ስልጣን መምጣት፤ በኢትዮጵያ ከሚነገሩ ከ 80 ገደማ ከሚሆኑ ቋንቋዎች ውስጥ አማርኛን ኦፊሴላዊ የሥራ ቋንቋ አድርጎታል። በስፋት አገልግሎት ላይ ከሚውሉ ቋንቋዎች ውስጥ ጥቂቱን ለመጥቀስ ያህል ትግርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ሶማሊኛ እና ሲዳምኛ ይገኙበታል።

የኢትዮጵያ ባህላዊው ከጤፍ በሚዘጋጀው እንጀራ ይታወቃል። ጤፍ ውስጥ ጠቃሚ ንጥረ ነገሮችን እና ማዕድናትን የሚያካትት ሲሆን ብዙውን ጊዜ ከተለያዩ የአትክልት ምግቦች እና ስጋዎች ጋር ይበላል።